የወባ በሽታ የሚያሳድረውን ሁለንተናዊ ተፅዕኖ ለመቀነስ ባለድርሻ አካላት ከመቼውም ጊዜ በላይ ትኩረት ሰጥተው ርብርብ ሊያደርጉ እንደሚገባ የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ ገለፁ!

ዋና አስተዳዳሪው ይህን ያሉት የዞኑ ጤና መምሪያ የወባ በሽታ ወረርሽኝ ለመከላከልና ለመቆጣጠር ያለመ የንቅናቄ መድረክ በወራቤ ከተማ ባካሄደበት ወቅት ነው።

ወራቤ   ጥቅምት 5/2017 ዓ.ም ፣ሰልጤ ዞን ኮሙኒኬሽን

መምሪያው በንቅናቄ መድረኩ ላይ የወባ በሽታ ስርጭትን በመከላከልና በመቆጣጠር ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት በማድረግ በሰፊው መክሯል። በንቅናቄ መድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ እንዳሉት የወባ በሽታ አርሶአደሩን ብሎም ህብረተሰቡን ከዕለተ ተዕለት ስራው የሚነጥል ነው። ይህም ወረርሽኙን ከወዲሁ መከላከልና መቆጣጠር ካልተቻለ በሀገር ብሎም በዞን ደረጃ በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚና ፖለቲካ የሚያሳድረው ተፅዕኖ ቀላል የሚባል አይደለም ብለዋል።


Read More

የወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአገልግሎት አሰጣጥ ይበል የሚያስብል ነው ሲሉ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ገለጹ!

ወራቤ  

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ም/ል ርዕሰ መስተዳድርና የት/ት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ፣ የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ፣ በኢፌድሪ ጤና ሚ/ር ሚኒስትር ድኤታ ዶ/ር ደረጀ ድጉማ የተመራ የሚ/ር መስሪያ ቤቱ የማኔጅመንት አካላት ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌና የማኔጅመንት አካላትና እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልን ጎብኝተዋል።


Read More

ትብብር ለላቀ ውጤት…

 

ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ - መስተዳድር ክቡር አቶ እንዳሻው ጣሰው ጋር በዘርፋችን ልዩ ትኩረት በሚጠይቁ ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ውይይት አካሂደናል፡፡ በውይይቱ በክህሎት ልማት፣ ሥራ ዕድል ፈጠራ እና ሰላማዊ ኢንዱስትሪ ግንኙነት ዙሪያ የተጀመሪ የሪፎርም ሥራዎችን በማስፋት በቀጣይ ዓመት የላቀ ውጤት ለማምጣትና በክልሉ የህብረተሰቡን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚቻልበትን ሁኔታ በዝርዝር ተመልክተናል፡፡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ - መስተዳድር ክቡር አቶ እንዳሻው ጣሰው የዘርፉ የሪፎርም ሥራዎች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አኳያ ያላቸውን ፋይዳ ከግምት ውስጥ በማስገባት ሥራውን ለመደገፍ ላሳዩን ቁርጠኝነት ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን ላቀርብ እወዳለሁ፡፡ የሥራ ባለቤት እርስዎ ነዎት! የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚንስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል በፌስቡክ ገጻቸው ያሰፈሩት መልዕክት!


Read More